የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
Directorate Director
አቶ ሓድጉ ፀሃየ

በቢሮው የተደራጀው የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት በቢሮው በሚከናወኑ ተግባራት ላይ የተደራጀ የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን ከዘርፉ የወረዱ ግቦች መነሻ በማድረግ ወጥነትና ተናባቢነት ባለው መልኩ በዋናነት ቢሮውን በተመለከቱ ጉዳዮች የህብረተሰባችን የመረጃ ፍላጎት ለማርካት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክት ዝግጅት፣ ክትትልና ሀብት ማፈላለግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክቶሬቱ የተቋቋመበት ዋና ምሰሶ እና ለቢሮው በአዋጅ ከተሰጡ ሥልጣንና ተግባር መካከል:- 1. ለችግር ተጋላጭ የሆኑ ሴቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች ህጻናትና ሌሎች ለጉዳት ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የኑሮ ሁኔታ የሚሻሻልበትን ሁኔታ ያጠናል፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ተግባራዊ ያደርጋል፤ 2. ሴቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ህጻናትና ሌሎች ለጉዳት ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በሚመለከት ከልማት ስትራቴጂ አኳያ ተቃኝቶ በወጣ ፕሮጀክት ላይ በከተማው ውስጥ ከሚሰሩ የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር ስምምነት ይመሰርታል፤ አፈፃፀማቸውን ይከታተላል፤ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ያቀርባል፤ 3. በማህበረሰብ አቀፍ ሊታቀፉና ሊደገፉ ያልቻሉ፣ በወንጀል ነክ ድርጊት ውስጥ የተሳተፉ፣ የሱስ ተጋላጭ ህጻናት፣ ጧሪና ደጋፊ የሌላቸው አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች እና ሰርቶ ለማደር አቅም የሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች በአስተዳደሩና መንግስታዊ ባልሆኑ ማዕከላት ውስጥ ክብካቤና ድጋፍ እንዲያገኙ ያደርጋል፤ 4. የማህበራዊ ልማት ፈንድ የሚያስገኝ ፕሮጀክት ያዘጋጃል፤ ሲፈቀድ ተግባራዊ ያደርጋል፤ 5. የሴቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ህጻናትና ሌሎች ለጉዳት ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በሁሉም የተባበረ ጥረት መፍትሄ እንዲያገኝ ያስተባብራል፤ ተፈፃሚነቱን ይከታተላል፤
Directorate Director's Message
በኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ስራ ህዝብንና መንግስትን በቀጥታ በማገናኘት የቢሮውን ተግባራት ውጤታማ በሚያደርግ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ እጅግ አስፈላጊ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ከቢሮው የስራ ባህሪ አኳያ ማህበረሰቡን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ በሚያነሳሳ መልኩ ጥቅም ላይ ማዋል የግድ ይላል፡፡ የፕሮጀክት ዝግጅት፣ ክትትልና ሀብት ማፈላለግ ዳይሬክቶሬት የጥናት፣ የሀብት አሰባሰብና የፕሮጀክት አፈፃፀም ሥርዓትን በማጠናከርና በማሳደግ የቢሮው ተገልጋይ የሆኑ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፤
Service under the directorate::
Nothing was found.